15. “አሮንና ልጆቹ መቅደሱንና ዕቃዎቹን፣ ንዋየ ቅዱሳቱንም በሙሉ ሸፍነው ከጨረሱ በኋላ ሰፈሩ ለመንቀሳቀስ ዝግጁ ሲሆን፣ ቀዓታውያን ለመሸከም ይምጡ፤ እንዳይሞቱ ግን ንዋየ ቅዱሳቱን መንካት የለባቸውም፤ ስለዚህ በመገናኛው ድንኳን ውስጥ ያሉትን እነዚህን ዕቃዎች የሚሸከሙ ቀዓታውያን ናቸው።
16. “የካህኑ የአሮን ልጅ አልዓዛር በመብራቱ ዘይት፣ ደስ የሚያሰኝ ሽታ ባለው ዕጣን፣ ዘወትር በሚቀርበው በእህል ቍርባንና በቅብዐ ዘይቱ ላይ ኀላፊነት ይኖረዋል፤ እንደዚሁም ማደሪያውንና በውስጡ ያለውን ሁሉ መቅደሱንና ዕቃዎቹን ጭምር ይጠብቃል።”
17. እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴንና አሮንን እንዲህ አላቸው፤
18. “የቀዓት ጐሣዎች ከሌዋውያን ተለይተው እንዳይጠፉ፤
19. ወደ ንዋየ ቅዱሳቱ በሚቀርቡበትም ጊዜ በሕይወት እንዲኖሩ እንጂ እንዳይሞቱ አንተ ይህን አድርግላቸው፤ አሮንና ልጆቹ ወደ መቅደሱ ይግቡ፤ እያንዳንዱንም ሰው በየሥራው ላይ ይደልድሉት፤ ምን መሸከም እንዳለበትም ያስታውቁት።
20. ቀዓታውያን ግን ንዋየ ቅዱሳቱን ለአንድ አፍታ እንኳን ለማየት አይግቡ፤ ቢገቡ ይሞታሉ።”
21. እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴን እንዲህ አለው፤
22. “ጌድሶናውያንንም በየቤተ ሰባቸውና በየጐሣቸው ቊጠራቸው፤