ዘኁልቍ 32:33-36 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

33. ከዚያም ሙሴ፣ የአሞራውያንን ንጉሥ የሴዎንን ግዛትና የባሳንን ንጉሥ የዐግን ግዛት ማለትም ምድሪቱንና ከነከተሞቿ በዙሪያዋ ያለውን ግዛት በሙሉ ለጋድና ለሮቤል ነገዶች እንዲሁም ለዮሴፍ ልጅ ለምናሴ ነገድ እኩሌታ ሰጣቸው።

34. የጋድ ልጆች፤ ዲቦንን፣ አጣሮትን፣ አሮዔርን፣

35. ዓጥሮትሾፋንን፣ ኢያዜርን፣ ዮግብሃን፣

36. ቤትነምራንና ቤትሃራንን የተመሸጉ ከተሞች አድርገው ሠሩአቸው፤ እንዲሁም ለበግና ለፍየል መንጎቻቸው ጒረኖዎች አበጁላቸው።

ዘኁልቍ 32