ዘኁልቍ 26:6-13 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

6. በአስሮን በኩል፣ የአስሮናውያን ጐሣ፤በከርሚ በኩል፣ የከርማውያን ጐሣ፤

7. እነዚህ የሮቤል ጐሣዎች ሲሆኑ፤ ከእነዚህም የተቈጠሩት አርባ ሦስት ሺህ ሰባት መቶ ሠላሳ ነበሩ።

8. የፈሉስ ልጅ ኤልያብ ሲሆን፣

9. የኤልያብ ልጆች ደግሞ፣ ነሙኤል ዳታንና አቤሮን ነበሩ። እነዚሁ ዳታንና አቤሮን በሙሴና በአሮን ላይ ያመፁ የማኅበሩ ሹማምት ሲሆኑ፣ ቆሬና ተከታዮቹ በእግዚአብሔር (ያህዌ) ላይ ባመፁ ጊዜ እነርሱም በነገሩ ነበሩበት።

10. ሁለት መቶ አምሳዎቹን ሰዎች እሳት በበላቻቸው ጊዜ የቆሬ ተከታዮች ሲሞቱ እነዚህን ደግሞ ምድር ተከፍታ ከእርሱ ጋር ዋጠቻቸው፤ መቀጣጫም ሆኑ፤

11. የቆሬ የዘር ሐረግ ግን አልጠፋም።

12. የስምዖን ዘሮች በየጐሣቸው እነዚህ ነበሩ፤በነሙኤል በኩል፣ የነሙኤላውያን ጐሣ፤በያሚን በኩል፣ የያሚናውያን ጐሣ፤በያኪን በኩል፣ የያኪናውያን ጐሣ፤

13. በዛራ በኩል፣ የዛራውያን ጐሣ፤በሳኡል በኩል፣ የሳኡላውያን ጐሣ፤

ዘኁልቍ 26