ዘኁልቍ 26:10-22 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

10. ሁለት መቶ አምሳዎቹን ሰዎች እሳት በበላቻቸው ጊዜ የቆሬ ተከታዮች ሲሞቱ እነዚህን ደግሞ ምድር ተከፍታ ከእርሱ ጋር ዋጠቻቸው፤ መቀጣጫም ሆኑ፤

11. የቆሬ የዘር ሐረግ ግን አልጠፋም።

12. የስምዖን ዘሮች በየጐሣቸው እነዚህ ነበሩ፤በነሙኤል በኩል፣ የነሙኤላውያን ጐሣ፤በያሚን በኩል፣ የያሚናውያን ጐሣ፤በያኪን በኩል፣ የያኪናውያን ጐሣ፤

13. በዛራ በኩል፣ የዛራውያን ጐሣ፤በሳኡል በኩል፣ የሳኡላውያን ጐሣ፤

14. እነዚህ የስምዖን ጐሣዎች ሲሆኑ፣ ከእነዚህ የተቈጠሩትም ሃያ ሁለት ሺህ ሁለት መቶ ነበሩ።

15. የጋድ ዘሮች በየጐሣዎቻቸው እነዚህ ነበሩ፤በጽፎን በኩል፣ የጽፎናውያን ጐሣ፤በሐጊ በኩል፣ የሐጋውያን ጐሣ፤በሹኒ በኩል፣ የሹናውያን ጐሣ፤

16. በኤስና በኩል፣ የኤስናናውያን ጐሣ፤በዔሪ በኩል፣ የዔራውያን ጐሣ፤

17. በአሮዲ በኩል፣ የአሮዳውያን ጐሣ፤በአርኤሊ በኩል፣ የአርኤላውያን ጐሣ፤

18. እነዚህ የጋድ ጐሣዎች ሲሆኑ፣ ከነዚህ የተቈጠሩት አርባ ሺህ አምስት መቶ ነበሩ።

19. ዔርና አውናን የይሁዳ ልጆች ነበሩ፤ ነገር ግን በከነዓን ምድር ሞተዋል።

20. የይሁዳ ዘሮች በየጐሣቸው እነዚህ ነበሩ፤በሴሎም በኩል፣ የሴሎማውያን ጐሣ፤በፋሬስ በኩል፣ የፋሬሳውያን ጐሣ፤በዛራ በኩል፣ የዛራውያን ጐሣ፤

21. የፋሬስ ዘሮች በየጐሣቸው እነዚህ ነበሩ፤በኤስሮም በኩል፣ የኤስሮማውያን ጐሣ፤በሐሙል በኩል፣ የሐሙላውያን ጐሣ፤

22. እነዚህ የይሁዳ ጐሣዎች ሲሆኑ፣ ከእነዚህ የተቈጠሩት ሰባ ስድስት ሺህ አምስት መቶ ነበሩ።

ዘኁልቍ 26