18. ኤዶም ግን እንዲህ ሲል መለሰ፤“በዚህ በኩል አታልፉም፤ እናልፋለን የምትሉ ከሆነ በሰልፍ ወጥተን በሰይፍ እንመታችኋለን።”
19. እስራኤላውያንም መልሰው፣“አውራውን መንገድ ይዘን እንሄዳለን፤ እኛም ሆንን ከብቶቻችን የትኛውንም ውሃችሁን ከጠጣን ዋጋውን እንከፍላለን፤ በእግር አልፈን መሄድ ብቻ እንጂ ሌላ ምንም አንፈልግም።” አሏቸው።
20. ኤዶምም እንደ ገና፣“በዚህ ማለፍ አትችሉም።” የሚል መልስ ሰጣቸው።ከዚያም ኤዶም ብዙና ኀይለኛ የሆነ ሰራዊት አሰልፎ ሊወጋቸው ወጣ፤
21. ስለዚህ ኤዶም በግዛቱ አልፈው እንዳይሄዱ ስለ ከለከላቸው እስራኤላውያን ተመለሱ።
22. መላው የእስራኤል ማኅበረሰብ ከቃዴስ ተነሥቶ ወደ ሖር ተራራ መጣ።
23. እግዚአብሔርም (ያህዌ) በኤዶም ወሰን አጠገብ ባለው በሖር ተራራ ሙሴንና አሮንን እንዲህ አላቸው፤
24. “አሮን ወደ ወገኖቹ ይሰበሰባል፤ ሁለታችሁም በመሪባ ውሃ በትእዛዜ ላይ ዐምፃችኋልና ለእስራኤላውያን ወደምሰጣት ምድር አይገባም።