ዘኁልቍ 2:24-30 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

24. በየሰራዊታቸው ሆነው ከኤፍሬም ምድብ የተመዘገቡት ወንዶች በሙሉ አንድ መቶ ስምንት ሺህ አንድ መቶ ናቸው፤ እነዚህ ሦስተኛ ሆነው ይመጣሉ።

25. “በሰሜን በኩል የዳን ምድብ ሰራዊት በዐርማው ሥር ይሆናል፤ የዳን ሕዝብ አለቃ የአሚሳዳይ ልጅ አኪዔዘር ሲሆን፣

26. የሰራዊቱም ብዛት ሥልሳ ሁለት ሺህ ሰባት መቶ ነው።

27. “የአሴር ነገድ ከእነዚህ ቀጥሎ ይሰፍራል፤ የአሴር ሕዝብ አለቃ የኤክራን ልጅ ፋግኤል ሲሆን፣

28. የሰራዊቱም ብዛት አርባ አንድ ሺህ አምስት መቶ ነው።

29. ከዚያም የንፍታሌም ነገድ ይቀጥላል፤ የንፍታሌም ሕዝብ አለቃ የዔናን ልጅ አኪሬ ሲሆን፣

30. የሰራዊቱም ብዛት አምሳ ሦስት ሺህ አራት መቶ ነው።

ዘኁልቍ 2