ዘኁልቍ 2:13-23 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

13. የሰራዊቱም ብዛት አምሳ ዘጠኝ ሺህ ሦስት መቶ ነው።

14. “ከዚያም የጋድ ነገድ ይቀጥላል፤ የጋድ ሕዝብ አለቃ የራጉኤል ልጅ ኤሊሳፍ ሲሆን፣

15. የሰራዊቱም ብዛት አርባ አምስት ሺህ ስድስት መቶ አምሳ ነው።

16. በየሰራዊታቸው ሆነው ከሮቤል ምድብ የተመዘገቡት ወንዶች በሙሉ አንድ መቶ አምሳ አንድ ሺህ አራት መቶ አምሳ ናቸው፤ እነዚህ ቀጥለው ይመጣሉ።

17. “ከዚህ በኋላ የመገናኛው ድንኳንና የሌዋውያን ምድብ በመካከል ሆነው ይጓዛሉ፤ እያንዳንዳቸውም አሰፋፈራቸውን በመከተል ቦታቸውን ጠብቀው በዐርማቸው ሥር ይጓዛሉ።

18. በምዕራብ በኩል የኤፍሬም ምድብ ሰራዊት በዐርማቸው ሥር ይሆናል፤ የኤፍሬም ሕዝብ አለቃ የዓሚሁድ ልጅ ኤሊሳማ ሲሆን፣

19. የሰራዊቱም ብዛት አርባ ሺህ አምስት መቶ ነው።

20. “ከእነዚህም የምናሴ ነገድ ይቀጥላል፣ የምናሴ ሕዝብ አለቃ የፍዳሱር ልጅ ገማልኤል ሲሆን፣

21. የሰራዊቱም ብዛት ሠላሳ ሁለት ሺህ ሁለት መቶ ነው።

22. ከዚያም የብንያም ነገድ ይቀጥላል፣ የብንያም ሕዝብ አለቃ የጋዴዮን ልጅ አቢዳን ሲሆን፣

23. የሰራዊቱም ብዛት ሠላሳ አምስት ሺህ አራት መቶ ነው።

ዘኁልቍ 2