ኤርምያስ 51:5-9 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

5. ምድራቸው በእስራኤል ቅዱስ ፊት፣በበደል የተሞላች ብትሆንም፣እስራኤልንና ይሁዳን አምላካቸው፣የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር አልጣላቸውም።

6. “ከባቢሎን ሸሽታችሁ ውጡፈጥናችሁም ሕይወታችሁን አትርፉ!በኀጢአቷ ምክንያት አትጥፉ። የእግዚአብሔር የበቀል ጊዜ ነው፤እርሱም የሥራዋን ይከፍላታል።

7. ባቢሎን በእግዚአብሔር እጅ የወርቅ ጽዋ ነበረች፤ምድርንም ሁሉ አሰከረች።ሕዝቦች ከወይን ጠጇ ጠጡ፤ስለዚህ አሁን አብደዋል።

8. ባቢሎን በድንገት ወድቃ ትሰበራለች፤ዋይ በሉላት!ምናልባት ልትፈወስ ስለምትችል፣ለቍስሏ የሚቀባ መድኀኒት ፈልጉላት።

9. “ ‘ባቢሎንን ለመፈወስ ሞክረን ነበር፤እርሷ ግን ልትፈወስ አትችልም፤ፍርዷ እስከ ሰማይ ስለ ደረሰ፣እስከ ደመናም ድረስ ከፍ ስላለ፣ትተናት ወደየአገራችን እንሂድ።’

ኤርምያስ 51