10. የባቢሎን ምድር ትዘረፋለች፤የሚዘርፏትም ሁሉ እስኪበቃቸው ይመዘብሩአታል፤”ይላል እግዚአብሔር።
11. “እናንተ ርስቴን የበዘበዛችሁ ሆይ፤ደስ ስላላችሁና ሐሤትም ስላደረጋችሁ፣በመስክ እንዳለች ጊደር ስለ ፈነጫችሁ፤እንደ ድንጒላ ፈረስ ስለ አሽካካችሁ፤
12. እናታችሁ እጅግ ታፍራለች፤የወለደቻችሁም ትዋረዳለች።እርሷም ምድረ በዳ፣ ደረቅ ምድርና በረሓ፣ከመንግሥታትም ሁሉ ያነሰች ትሆናለች።
13. ከእግዚአብሔር ቍጣ የተነሣ ባድማ ትሆናለች እንጂ፣የሚኖርባት አይገኝም፤በቍስሎችዋም ሁሉ ምክንያት፣በባቢሎን የሚያልፍ ሁሉ ይገረማል፤ ያፌዝባታልም።