6. ሽሹ፤ ሕይወታችሁንም አትርፉ!በምድረ በዳ እንዳለ ቍጥቋጦ ሁኑ።
7. በድርጊታችሁና በብልጽግናችሁ ስለምትታመኑ፣እናንተም ትማረካላችሁ፣ካሞሽም ከካህናቱና ከመኳንንቱ ጋር፣በምርኮ ይወሰዳል።
8. በእያንዳንዱ ከተማ ላይ አጥፊ ይመጣል፤አንድም ከተማ አያመልጥም። እግዚአብሔር ተናግሮአልና፣ሸለቆው ይጠፋል፤ዐምባውም ይፈርሳል።
9. በራ እንድታመልጥ፣ለሞዓብ ክንፍ ስጧት፤ከተሞቿም ምንም እስከማይኖርባቸው ድረስ፣ባድማ ይሆናሉ።
10. “የእግዚአብሔርን ሥራ በቸልታ የሚያከናውን ርጉም ይሁን፤ሰይፉን ደም ከማፍሰስ የሚከላከል የተረገመ ይሁን፤
11. “ሞዓብ በአምቡላው ላይ እንዳረፈ የወይን ጠጅ፣ከልጅነት ጀምሮ የተረጋጋ ነበረ፤ከዕቃ ወደ ዕቃ አልተገላበጠም፤በምርኮም አልተወሰደም፤ቃናው እንዳለ ነው፤መዐዛውም አልተለወጠም።