5. እንደ ገናም በሰማርያ ኰረብቶች ላይ፣ወይን ትተክያለሽ፤አትክልተኞች ይተክሏቸዋል፤በፍሬውም ደስ ይላቸዋል።
6. ጠባቂዎች፣ በኤፍሬም ኰረብቶች ላይ፣‘ኑ፤ ወደ ጽዮን፣ወደ አምላካችን ወደ እግዚአብሔር እንውጣ!’ብለው የሚጮኹበት ቀን ይመጣል።
7. እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤“ስለ ያዕቆብ በደስታ ዘምሩ፤ስለ ሕዝቦች አለቃ እልል በሉ፤ምስጋናችሁን አሰሙ፤‘እግዚአብሔር ሆይ፤ የእስራኤልን ቅሬታ፣ሕዝብህን አድን’ በሉ።