6. ጳስኮር ሆይ፤ አንተና በቤትህ የሚኖሩት ሁሉ ወደ ባቢሎን ትጋዛላችሁ። አንተና በሐሰት ትንቢት የተነበይህላቸው ባልንጆሮችህ በዚያ ትሞታላችሁ፤ በዚያም ትቀበራላችሁ።’ ”
7. እግዚአብሔር ሆይ፤ አታለልኸኝ፤ እኔም ተታለልሁ፤አንተ ከእኔ እጅግ በረታህ፤ አሸነፍህም፤ቀኑን ሙሉ ማላገጫ ሆንሁ፤ሁሉም ተዘባበቱብኝ።
8. በተናገርሁ ቍጥር እጮኻለሁ፤“ሁከትና ጥፋት!” ብዬ ዐውጃለሁ፤ስለዚህ የእግዚአብሔር ቃል፣ቀኑን ሙሉ ስድብና ነቀፋ አስከተለብኝ።
9. ነገር ግን፣ “ከእንግዲህ የእርሱን ስም አላነሣም፤በስሙም አልናገርም” ብል፣ቃሉ በልቤ እንደ እሳት፣በዐጥንቴም ውስጥ እንደ ረመጥ ሆነብኝ፤ዐፍኜ መያዝ አቃተኝ፤ጨርሶ መቋቋም አልቻልሁም።
10. “በየቦታው ሽብር አለ፤አውግዙት፤ እናውግዘው፤”ብለው ብዙ ሲያንሾካሽኩ ሰማሁ፤መውደቄን በመጠባበቅ፣ባልንጀሮቼ የነበሩ ሁሉ፣“ይታለል ይሆናል፣ከዚያም እናሸንፈዋለን፤እንበቀለዋለንም” ይላሉ።