ኢዮብ 34:1-6 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

1. ኤሊሁ በመቀጠል እንዲህ አለ፤

2. “እናንት ጠቢባን፣ ቃሌን ስሙ፤ዐዋቂዎችም አድምጡኝ።

3. ምላስ ምግብን አጣጥሞ እንደሚለይ፣ጆሮም የንግግርን ለዛ ለይቶ ያውቃል።

4. የሚበጀንን እንምረጥ፣መልካሙንም አብረን እንወቅ።

5. “ኢዮብ እንዲህ ይላል፤ ‘እኔ ንጹሕ ነኝ፤እግዚአብሔር ግን ፍትሕ ነሣኝ፤

6. እውነተኛ ብሆንም፣እንደ ውሸታም ተቈጥሬአለሁ፤በደል ባይኖርብኝም፣በማይፈወስ ቍስል ተመትቻለሁ።’

ኢዮብ 34