32. ነገር ግን ቤቴ ለመንገደኛው ዘወትር ክፍት ስለ ነበር፣መጻተኛው በጐዳና ላይ አያድርም ነበር።
33. ሰዎች እንደሚያደርጉት በደሌን በልቤ በመሰወር፤ኀጢአቴን ሸሽጌ ከሆነ፣
34. ሕዝቡን በመፍራት፣የወገኖቼንም ንቀት በመሸሽ፣ወደ ደጅ ሳልወጣ፣ ዝም ብዬ ቤት ውስጥ አልተቀመጥሁም።
35. “ምነው የሚሰማኝ ባገኝ!የመከላከያ ፊርማዬ እነሆ፤ ሁሉን የሚችል አምላክ ይመልስልኝ፤ከሳሼም ክሱን በጽሑፍ ያቅርብ።