ኢዮብ 3:3-9 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

3. “የተወለድሁበት ቀን ይጥፋ፣‘ወንድ ልጅ ተፀነሰ’ የተባለበት ሌሊት።

4. ያ ቀን ጨለማ ይሁን፤እግዚአብሔር ከላይ አይመልከተው፤ብርሃንም አይብራበት።

5. ጨለማና የሞት ጥላ ይውረሱት፤ደመናም በላዩ ላይ ይረፍ፤ብርሃኑን ጽልመት ይዋጠው።

6. ያ ሌሊት በድቅድቅ ጨለማ ይያዝ፤ከዓመቱ ቀናት ጋር አይቈጠር፤ከወራቱ በአንዱም ውስጥ አይግባ።

7. ያ ሌሊት መካን ይሁን፤እልልታም አይሰማበት።

8. ሌዋታንን ለማነሣሣት የተዘጋጁ፤ቀንንም የሚረግሙ ያን ቀን ይርገሙት።

9. አጥቢያ ኮከቦቹ ይጨልሙ፤ብርሃንን እየጠበቀ ይጣ፣የንጋት ጮራ ሲፈነጥቅ አይይ።

ኢዮብ 3