ኢዮብ 14:6-10 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

6. እንግዲህ ዘመኑን እንደ ምንደኛ እስኪፈጽም ድረስ፣ፊትህን ከእርሱ መልስ፤ ተወው።

7. “ዛፍ እንኳ ቢቈረጥ፣እንደ ገና ሊያቈጠቍጥ፣አዳዲስ ቅርንጫፍም ሊያበቅል ተስፋ አለው።

8. ሥሩ በምድር ውስጥ ቢያረጅጒቶው በመሬት ውስጥ ቢበሰብስም፣

9. የውሃ ሽታ ባገኘ ጊዜ ያቈጠቍጣል፤እንደ ተተከለም ችግኝ ቅርንጫፍ ያወጣል።

10. ሰው ግን ይሞታል፤ ክንዱንም ይንተራሳል፤ነፍሱም ትወጣለች፤ ከእንግዲህስ የት ይገኛል?

ኢዮብ 14