6. የቀማኞች ድንኳን አይታወክም፤አምላካቸውን በእጃቸው ይዘው እየዞሩም፣እግዚአብሔርንም እያስቈጡ በሰላም ይኖራሉ።
7. “እስቲ እንስሶችን ጠይቁ፤ ያስተምሯችኋል፤የሰማይ ወፎችንም ጠይቁ፣ ይነግሯችኋል፤
8. ለምድር ተናገሩ፤ ታስተምራችኋለች፤የባሕርም ዓሣ ይነግራችኋል።
9. የእግዚአብሔር እጅ ይህን እንዳደረገ፣ከእነዚህ ሁሉ የማያውቅ ማን ነው?
10. የፍጥረት ሁሉ ሕይወት፣የሰውም ሁሉ መንፈስ በእጁ ናትና፤
11. ምላስ የምግብን ጣዕም እንደሚለይ፣ጆሮ ቃላትን አይለይምን?