37. ቃዴስ፣ ኤድራይ፣ ዐይንሐጾር፣
38. ይርኦን፣ ሚግዳልኤል፣ ሖሬም፣ ቤትዓናትና ቤትሳሚስ። እነዚህ ከነ መንደሮቻቸው ዐሥራ ዘጠኝ ከተሞች ናቸው።
39. እነዚህ ለንፍታሌም ነገድ ርስት ሆነው በየጐሣው የተደለደሉ ከተሞችና መንደሮች ነበሩ።
40. ሰባተኛው ዕጣ ለዳን ነገድ በየጐሣው ወጣ፤
41. የወረሱትም ምድር የሚከተሉትን ያካትታል፤ጾርዓ፣ ኤሽታኦል፣ ዒርሼሜሽ፣
42. ሸዕለቢን፣ ኤሎን፣ ይትላ፣
43. ኤሎን፣ ተምና፣ አቃሮን፣
44. ኢልተቄ፣ ገባቶን፣ ባዕላት፣
45. ይሁድ፣ ብኔብረቅ፣ ጋትሪሞን፣