1. ሁለተኛው ዕጣ ለስምዖን ነገድ በየጐሣ በየጐሣው ወጣ፤ ርስታቸውም ዙሪያውን በይሁዳ ነገድ ርስት የተከበበ ነበር፤
2. ይህም የሚከተሉትን ያካትታል፤ ቤርሳቤህ፣ ሤባ፣ ሞላዳ፣
3. ሐጸር ሹዓል፣ ባላ፣ ዔጼም፣
4. ኤልቶላድ፣ በቱል፣ ሔርማ፣
5. ጺቅላግ፣ ቤትማርካቦት፣ ሐጸርሱሳ፣
6. ቤተለባኦትና ሻሩሔን ነበሩ፤ እነዚህ ዐሥራ ሦስት ከተሞችና መንደሮቻቸው ናቸው።
7. ዓይን፣ ሪሞን፣ ዔቴርና ዓሻን የተባሉት አራት ከተሞቻቸውና መንደሮቻቸው፣
8. ደግሞም እስከ ባዕላትብኤር ወይም ኔጌብ ውስጥ እስካለው እስከ ራማት ድረስ ባሉት ከተሞች ዙሪያ የሚገኙት መንደሮች ሁሉ ከእነዚሁ ጋር ይጠቃለላሉ።እንግዲህ በየጐሣው የተደለደለው የስምዖን ነገድ ርስት ይህ ነበር።
9. የይሁዳ ነገድ የያዘው ርስት እጅግ ሰፊ ስለ ነበር፣ ከይሁዳ ነገድ ድርሻ ተከፍሎ ለስምዖን ነገድ በርስትነት ተሰጠ፤ ከዚህ የተነሣም የስምዖን ነገድ በይሁዳ ነገድ ድርሻ ርስት ሊካፈል ቻለ።
10. ሦስተኛው ዕጣ ለዛብሎን ነገድ በየጐሣ በየጐሣው ወጣ፤የርስታቸውም ድንበር እስከ ሣሪድ ይደርሳል፤
11. ወደ ምዕራብም በመሄድ በመርዓላ በኩል ያልፋል፤ ደባሼትን ተጠግቶም በዮቅንዓም አጠገብ እስካለው ወንዝ ድረስ ይዘልቃል።