ኢያሱ 18:20-28 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

20. በምሥራቅ በኩል ያለው ድንበር፣ ራሱ የዮርዳኖስ ወንዝ ነው።ይህ እንግዲህ የብንያም ነገድ ጐሣዎች በርስትነት የወረሷት ምድር ዳር ድንበሮቿ ሁሉ እነዚህ ነበሩ።

21. የብንያም ነገድ በየጐሣቸው የያዟቸው ከተሞች እነዚህ ናቸው፤ ኢያሪኮ፣ ቤትሖግላ፣ ዓመቀጺጽ፣

22. ቤትዓረባ፣ ዘማራይም፣ ቤቴል፣

23. ዓዊም፣ ፋራ፣ ኤፍራታ፣

24. ክፊርዓሞናይ፣ ዖፍኒ እንዲሁም ጋባ ናቸው፤ እነዚህም ከነ መንደሮቻቸው ዐሥራ ሁለት ከተሞች ናቸው።

25. ገባዖን፣ ራማ፣ ብኤሮት፣

26. ምጽጳ፣ ከፊራ፣ አሞቂ፣

27. ሬቄም፣ ይርጵኤል፣ ተርአላ፣

28. ጼላ፣ ኤሌፍ፣ የኢያቡሳውያን ከተማ ኢየሩሳሌም፣ ጊብዓ እንዲሁም ቂርያት ነበሩ፤ እነዚህም ከነ መንደሮቻቸው ዐሥራ አራት ከተሞች ናቸው።እንግዲህ የብንያም ነገድ በየጐሣቸው የወረሱት ይህ ነበር።

ኢያሱ 18