ኢያሱ 18:17-28 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

17. ደግሞም ወደ ሰሜን ይታጠፍና በቤትሳሚስ በኩል አድርጎ እስከ ጌሊሎት ይዘልቃል፤ ከዚያም በአዱሚም መተላለፊያ ትይዩ እስካለው እስከ ሮቤል ልጅ እስከ ቦሀን ድንጋይ ይወርዳል።

18. ወደ ቤትዓረባ ሰሜናዊ ተረተር በመቀጠል ቊልቊል ወደ ዐረባ ይወርዳል።

19. ከዚያም ሰሜናዊን የቤትሖግላንን ተረተር አልፎ ይሄድና በስተ ደቡብ የዮርዳኖስ ወንዝ እስከሚገባበት እስከ ሙት የባሕር ወሽመጥ ይዘልቃል፤ ይህም ደቡባዊ ድንበሩ ነው።

20. በምሥራቅ በኩል ያለው ድንበር፣ ራሱ የዮርዳኖስ ወንዝ ነው።ይህ እንግዲህ የብንያም ነገድ ጐሣዎች በርስትነት የወረሷት ምድር ዳር ድንበሮቿ ሁሉ እነዚህ ነበሩ።

21. የብንያም ነገድ በየጐሣቸው የያዟቸው ከተሞች እነዚህ ናቸው፤ ኢያሪኮ፣ ቤትሖግላ፣ ዓመቀጺጽ፣

22. ቤትዓረባ፣ ዘማራይም፣ ቤቴል፣

23. ዓዊም፣ ፋራ፣ ኤፍራታ፣

24. ክፊርዓሞናይ፣ ዖፍኒ እንዲሁም ጋባ ናቸው፤ እነዚህም ከነ መንደሮቻቸው ዐሥራ ሁለት ከተሞች ናቸው።

25. ገባዖን፣ ራማ፣ ብኤሮት፣

26. ምጽጳ፣ ከፊራ፣ አሞቂ፣

27. ሬቄም፣ ይርጵኤል፣ ተርአላ፣

28. ጼላ፣ ኤሌፍ፣ የኢያቡሳውያን ከተማ ኢየሩሳሌም፣ ጊብዓ እንዲሁም ቂርያት ነበሩ፤ እነዚህም ከነ መንደሮቻቸው ዐሥራ አራት ከተሞች ናቸው።እንግዲህ የብንያም ነገድ በየጐሣቸው የወረሱት ይህ ነበር።

ኢያሱ 18