16. ድንበራቸው ከአርኖን ሸለቆ ዳርቻ ካለው ከአሮዔርና ከሸለቆው መካከል ካለችው ከተማ አንሥቶ ያለው ግዛት ሲሆን፣ ሜድባ አጠገብ ያለውን ደጋውን አገር በሙሉ፣
17. ሐሴቦንና በደጋው ላይ ያሉትን ከተሞችዋን በሙሉ፣ እንዲሁም ዲቦንን፣ ባሞትባኣልን፣ ቤትበኣልምዖን፣
18. ያሀጽን፣ ቅዴሞትን፣ ሜፍዓትን፣
19. ቂርያታያምን፣ ሴባማን፣ በሸለቆው ኰረብታ ላይ ያለችውን ጼሬትሻሐርን፣
20. ቤተፌጎርን፣ የፈስጋን ሸንተረሮችና ቤትየሺሞትን፣