8. የሰላምን መንገድ አያውቁም፤በጐዳናቸውም ፍትሕ የለም፤መንገዳቸውን ጠማማ አድርገውታል፤በዚያም የሚሄድ ሰላም አያገኝም።
9. ስለዚህ ፍትሕ ከእኛ ርቆአል፤ጽድቅም ወደ እኛ አይመጣም፤ብርሃንን ፈለግን፤ ነገር ግን ሁሉ ጨለማ ነው፤የብርሃንን ጸዳል ፈለግን፤ የምንሄደው ግን በድንግዝግዝታ ነው።
10. በቅጥሩ ላይ እንደ ዕውር ተደናበርን፤አካሄዳችንም ዐይን እንደሌላቸው በዳበሳ ሆነ፤ጀምበር በምትጠልቅበት ጊዜ እንደሚሆነው በእኩለ ቀን ተደናበርን፤በብርቱዎች መካከልም እንደ ሙታን ሆንን።