26. ከሩቅ ያሉትን ሕዝቦች የሚጠራበትንምልክት ያቆማል፤ከምድር ዳርቻም በፉጨት ይጠራቸዋል፤እነርሱም እየተጣደፉ በፍጥነት ይመጣሉ።
27. በመካከላቸው ደካማና ስንኩል አይገኝም፤የሚያንቀላፋና የሚተኛ አይኖርም፤የወገባቸው መቀነት አይላላም፤የጫማቸውም ማሰሪያ አይበጠስም።
28. ፍላጻቸው የተሳለ፣ቀስታቸውም የተደገነ ነው፤የሠረገሎቻቸውም መንኰራኵሮች እንደዐውሎ ነፋስ ናቸው።
29. ጩኸታቸው እንደ አንበሳ ነው፤እንደ አንበሳ ደቦል ያገሣሉ፤ያደኑትንም ይዘው ይጮኻሉ፤ተሸክመውት ይሄዳሉ፤ የሚያስጥልም የለም።
30. በዚያን ቀንእንደ ባሕር ሞገድ ይጮኹበታል፤ማንም ወደ ምድር ቢመለከት፣ጨለማንና መከራን ያያል፤ብርሃን እንኳ በደመናዎች ይጋረዳል።