15. እኔ፣ እኔው ራሴ ተናግሬአለሁ፤በርግጥ እኔ ጠርቼዋለሁ፤አመጣዋለሁ፤ሥራውም ይከናወንለታል።
16. “ወደ እኔ ቅረቡ፤ ይህን ስሙ፤“ከመጀመሪያ ጀምሮ በስውር አልተናገርሁም፤ሲፈጸምም እኔ እዚያው ነበርሁ።”አሁንም ጌታ እግዚአብሔርና መንፈሱልከውኛል።
17. የተቤዠህ፣ የእስራኤል ቅዱስ፣ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤“እኔ እግዚአብሔር አምላክህ፣የሚበጅህ ምን እንደሆነ የማስተምርህ፣መሄድ በሚገባህ መንገድ የምመራህ ነኝ።
18. ትእዛዜን ሰምተህ ብቻ ቢሆን ኖሮ፣ሰላምህ እንደ ወንዝ፣ጽድቅህም እንደ ባሕር ሞገድ በሆነ ነበር።