ኢሳይያስ 44:14-19 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

14. ዝግባ ይቈርጣል፤ሾላ ወይም ዋንዛ ይመርጣል፤በደን ውስጥ ካሉት ዛፎች ጋር እንዲያድግ ይተወዋል፤ወይም ጥድን ይተክላል፤ ያንንም ዝናም ያሳድገዋል።

15. ሰው ለማገዶ ይጠቀምበታል፤ከዚያም ጥቂት ወስዶ በማንደድ ይሞቀዋል፤እንጀራም ይጋግርበታል።ከዚሁ ጠርቦ አምላክ ያበጃል፤ያመልከዋል፤ጣዖትን ይሠራል፤ ወድቆም ይሰግድለታል።

16. ግማሹን ዕንጨት ያነደዋል፤በላዩ ምግቡን ያበስልበታል፤ሥጋ ጠብሶበት እስኪጠግብ ይበላል፤እሳቱን እየሞቀ እንዲህ ይላል፤“እሰይ ሞቀኝ፤ እሳቱም ይታየኛል።”

17. በቀረው ዕንጨት የጣዖት አምላኩን ይሠራበታል፤ወድቆ ይሰግድለታል፤ ያመልከዋል፤ወደ እርሱም እየጸለየ፣“አንተ አምላኬ ነህ፤ አድነኝ” ይላል።

18. ምንም አያውቁም፤ አያስተውሉም፤እንዳያዩ ዐይናቸው ተሸፍኖአል፤እንዳያስተውሉ ልባቸው ተዘግቶአል።

19. ማንም ቆም ብሎ አላሰበም፤ዕውቀት ወይም ማስተዋል ስለሌለው እንዲህ ማለት አልቻለም፤“ግማሹን በእሳት አቃጥዬዋለሁ፤በፍሙ እንጀራ ጋግሬበታለሁ፤ሥጋ ጠብሼበት በልቻለሁ፤ታዲያ፣ በቀረው እንዴት ጸያፍ ነገር እሠራለሁ?ለግንድስ መስገድ ይገባኛልን?”

ኢሳይያስ 44