3. እኔ እግዚአብሔር አምላክህ፣የእስራኤልም ቅዱስ መድኀኒትህ ነኝና፤ግብፅን ለአንተ ቤዛ እንድትሆን፣ኢትዮጵያንና ሳባን በአንተ ፈንታ እሰጣለሁ።
4. ለዐይኔ ብርቅና ክቡርም ስለ ሆንህ፣እኔም ስለምወድህ፣ሰዎችን በአንተ ምትክ፣ሕዝቦችንም በሕይወትህ ፈንታ እሰጣለሁ።
5. ከአንተ ጋር ነኝና አትፍራ፤ልጆችህን ከምሥራቅ አመጣለሁ፤ከምዕራብም እሰበስብሃለሁ።
6. ሰሜንን፣ ‘አምጣ’፣ደቡብንም፣ ‘ልቀቅ’ እላለሁ፤ወንዶች ልጆቼን ከሩቅ፣ሴቶች ልጆቼንም ከምድር ዳርቻ፣