ኢሳይያስ 29:3-7 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

3. በዙሪያሽ እሰፍራለሁ፤በቅጥር እከብሻለሁ፤የከበባ ዐምባም ሠርቼ አስጨንቅሻለሁ።

4. ወደ ታች ትወርጃለሽ፤ ከምድርም በታች ትናገሪያለሽ፤ንግግርሽ ከትቢያ እየተጒተመተመ ይወጣል፤ድምፅሽ እንደ መናፍስት ድምፅ ከመሬት ወደ ላይ ይመጣል፤ንግግርሽ ከትቢያ ያንሾካሹካል።

5. ነገር ግን ብዙ ጠላቶችሽ እንደ ትቢያ ብናኝ፣መንጋ ጨካኞችም በነፋስ እንደሚነጻገለባ ይሆናሉ።ድንገት ሳይታሰብም፣

6. የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር፣በነጐድጓድ፣ በምድር መናወጥና በታላቅ ድምፅ፣በዐውሎ ነፋስና በኀይለኛ ሞገድ ፈጽሞ በሚባላም የእሳት ነበልባል ይመጣል።

7. አርኤልን የሚወጋ የአሕዛብ ሁሉ መንጋ፣በእርሷና በምሽጓ ላይ አደጋ የሚጥልና የሚከባት፣እንደ ሕልምበሌሊትም እንደሚታይ ራእይ ይሆናል።

ኢሳይያስ 29