4. ልቤ ተናወጠ፤ፍርሀት አንቀጠቀጠኝ፤የጓጓሁለት ውጋጋን፣ታላቅ ፍርሀት አሳደረብኝ።
5. ማእዱን አሰናዱ፤ምንጣፉን አነጠፉ፤በሉ፤ ጠጡ!እናንት ሹማምት ተነሡ፤ጋሻውን በዘይት ወልውሉ!
6. ጌታ እንዲህ አለኝ፤“ሂድ፤ ጠባቂ አቁም፤ያየውንም ይናገር፤
7. በፈረሶች የሚሳብ፣ሠረገሎችን ሲያይ፣በአህያ ላይ የሚቀመጡትን፣በግመል የሚጋልቡትን ሲመለከት፣ያስተውል፣በጥንቃቄም ያስተውል።”
8. ጠባቂው ጮኸ፤ እንዲህም አለ፤“ጌታ ሆይ፤ በየቀኑ ማማ ላይ ቆሜአለሁ፤በየሌሊቱም በቦታዬ አለሁ።
9. እነሆ፤ አንድ ሰው በፈረሶች በሚሳብበሠረገላ መጥቶአል፤እንዲህም ሲል መለሰ፣‘ባቢሎን ወደቀች፣ ወደቀየአማልክቷም ምስሎች ሁሉ፣ተሰባብረው ምድር ላይ ወደቁ።’ ”
10. በዐውድማ ላይ የተወቃህ ሕዝቤ ሆይ፤ከሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር፣ከእስራኤል አምላክ፣የሰማሁትን እነግርሃለሁ።
11. ስለ ኤዶም የተነገረ ንግር፤አንዱ ከሴይር ጠርቶኝ፣“ጠባቂ ሆይ፤ ሊነጋ ምን ያህል ቀረው?ጠባቂ ሆይ፤ ሊነጋ ምን ያህል ቀረው?” አለኝ።