11. የእብሪተኛ ሰው ዐይን ይሰበራል፤የሰዎችም ትዕቢት ይዋረዳል፤በዚያን ቀን እግዚአብሔር ብቻውን ከፍ ከፍ ይላል።
12. የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔርእብሪተኛውንና ትዕቢተኛውን ሁሉ፣የተኵራራውን በሙሉየሚያዋርድበት ቀን አለው።
13. ረዥምና ከፍ ከፍ ያሉትን የሊባኖስ ዝግባዎች ሁሉ፣የባሳንን የወርካ ዛፎች ሁሉ፣
14. ታላላቁን ተራራ ሁሉ፣ከፍ ያለው ኰረብታ ሁሉ፣
15. ረጃጅሙን ግንብ ሁሉ፣የተመሸገውን ቅጥር ሁሉ፣