17. መልካም ማድረግን ተማሩ፤ፍትሕን እሹ፣የተገፉትን አጽናኑ፤አባት ለሌላቸው ቁሙላቸው፤ለመበለቶችም ተሟገቱ።
18. “ኑና እንዋቀስ”ይላል እግዚአብሔር፤“ኀጢአታችሁ እንደ ዐለላ ቢቀላእንደ በረዶ ይነጣል፤እንደ ደም ቢቀላምእንደ ባዘቶ ነጭ ይሆናል።
19. እሺ ብትሉ፣ ብትታዘዙምየምድርን በረከት ትበላላችሁ፤
20. እምቢ ብላችሁ ብታምፁ ግንሰይፍ ይበላችኋል።” የእግዚአብሔር አፍ ይህን ተናግሮአልና።
21. ታማኝ የነበረችው ከተማእንዴት አመንዝራ እንደሆነች ተመልከቱቀድሞ ፍትሕ የሞላባት፣ጽድቅ የሰፈነባት ነበረች፤አሁን ግን የነፍሰ ገዳዮች ማደሪያ ሆነ