17. ነገር ግን በጽዮን ተራራ ነጻ መውጣት ይሆናል፤የያዕቆብ ቤትም እርሷ የተቀደሰች ትሆናለች፤ርስታቸውን ይወርሳሉ።
18. የያዕቆብ ቤት እሳት፣የዮሴፍም ቤት ነበልባል ይሆናል፤የዔሳው ቤት ገለባ ይሆናል፤ያቃጥሉታል፤ ይበሉትማል፤ከዔሳው ቤት የሚተርፍ፣ አይኖርም።” እግዚአብሔር ተናግሮአል።
19. የኔጌብ ሰዎች፣የዔሳውን ተራራ ይይዛሉ፤ከተራራው ግርጌ ያሉ ሰዎችም፣የፍልስጥኤማውያንን ምድር ይወርሳሉ፤የኤፍሬምንና የሰማርያንም ዕርሻ ይይዛሉ፤ብንያምም ገለዓድን ይወርሳል።