1. ከሰላትያል ልጅ ከዘሩባቤልና ከኢያሱ ጋር የተመለሱት ካህናትና ሌዋውያን እነዚህ ነበሩ፤ሠራያ፣ ኤርምያስ፣ ዕዝራ፣
2. አማርያ፣ መሉክ፣ ሐጡስ፣
3. ሴኬንያ፣ ሬሁም፣ ሜሪሞት፣
4. አዶ፣ ጌንቶን፣ አብያ፣
5. ሚያሚን፣ መዓድያ፣ ቢልጋ፣
6. ሸማያ፣ ዮያሪብ፣ ዮዳኤ፣
7. ሰሉ፣ ዓሞቅ፣ ኬልቅያስና ዮዳኤ።እነዚህ በኢያሱ ዘመን የካህናቱና የወንድሞቻቸው አለቆች ነበሩ።
8. ሌዋውያኑ ደግሞ ኢያሱ፣ ቢንዊ፣ ቀድምኤል፣ ሰራብያ፣ ይሁዳ እንዲሁም ከወንድሞቹ ጋር የምስጋና መዝሙር ኀላፊ የሆነው መታንያ ነበሩ።
9. ወንድሞቻቸው የሆኑት በቅቡቅያና ዑኒም በአገልግሎት ጊዜ ከእነርሱ ትይዩ ይቆሙ ነበር።
10. ኢያሱ ዮአቂምን ወለደ፤ ዮአቂም ኤልያሴብን ወለደ፤ ኤልያሴብ ዮአዳን ወለደ፤
11. ዮአዳ ዮናታንን ወለደ፤ ዮናታንም ያዱአን ወለደ።
12. በዮአቂም ዘመን የካህናቱ ቤተ ሰብ አለቆች እነዚህ ነበሩ፤ከሠራያ ቤተ ሰብ፣ ምራያ፤ከኤርምያስ፣ ሐናንያ፤
13. ከዕዝራ፣ ሜሱላም፤ከአማርያ፣ ይሆሐናን፤
14. ከሙሊኪ፣ ዮናታን፤ከሰብንያ፣ ዮሴፍ፤
15. ከካሪም፣ ዓድና፤ከመራዮት፣ ሔልቃይ፤
16. ከአዶ፣ ዘካርያስ፤ከጌንቶን፣ ሜሱላም፤