24. የይሁዳ ልጅ የዛራ ዘር የሆነው የሜሴዜቤል ልጅ ፈታያ ሕዝቡን በሚመለከት ጒዳይ ሁሉ የንጉሡ ተወካይ ነበር።
25. ከይሁዳ ሕዝብ ጥቂቱ በመንደሮችና በእርሻ ቦታዎች፣ በቂርያት አርባቅና በዙሪያዋ ባሉ መኖሪያዎቿ፣ በዲቦንና በመኖሪያዎቿ፣ በይቀብጽኤልና በመንደሮቿ ተቀመጡ፤
26. በኢያሱ፣ በሞላዳ፣ በቤትጳሌጥ፣
27. በሐጸርሹዓል፣ በቤርሳቤህና በመኖሪያዎቿ፣
28. በጺቅላግ፣ በምኮናና በመኖሪያዎቿ፣
29. በዓይንሪሞን፣ በጾርዓ፣ በየርሙት፣
30. በዛኖዋ፣ በዓዶላምና በመንደሮቻቸው፣ በለኪሶና በእርሻዎቿ፣ በዓዜቃና በመንደሮቿ። ስለዚህ ከቤርሳቤህ ጀምሮ እስከ ሄኖም ሸለቆ ባለው ስፍራ ሁሉ ተቀመጡ።