6. የጽዮን ሴት ልጅ፣ግርማ ሞገሷ ሁሉ ተለይቶአታል፤መሳፍንቶቿ፣መሰማሪያ እንዳጣ ዋልያ ናቸው፤በአሳዳጆቻቸው ፊት፣በድካም ሸሹ።
7. በተጨነቀችባቸውና በተንከራ ተተችባቸው ቀናት፣ኢየሩሳሌም በጥንት ዘመን የነበራትን፣ሀብት ሁሉ ታስባለች፤ሕዝቦቿ በጠላት እጅ በወደቁ ጊዜ፣የረዳት ማንም አልነበረም፤ጠላቶቿ ተመለከቷት፤በመፈራረሷም ሣቁ።
8. ኢየሩሳሌም ከባድ ኀጢአት ሠርታለች፤ስለዚህም የረከሰች ሆናለች፤ያከበሯት ሁሉ ናቋት፤ዕራቍቷን ሆና አይተዋታልና፤እርሷ ራሷ ታጒረመርማለች፤ወደ ኋላዋም ዘወር ብላለች።
9. ርኵሰቷ በቀሚሷ ላይ ታየ፤ ወደ ፊት የሚሆንባትን አላሰበችም፤አወዳደቋ አስደንጋጭ ሆነ፤የሚያጽናናትም አልነበረም፤“እግዚአብሔር ሆይ፤ መከራዬንተመልከት፤ጠላት ድል አድርጎአልና!”
10. በሀብቷ ሁሉ ላይ፣ጠላት እጁን ዘረጋ፤ወደ ጉባኤህ እንዳይገቡ፣የከለከልሀቸው፣ጣዖት የሚያመልኩ አሕዛብ፣ወደ መቅደሷ ሲገቡ አየች።
11. እንጀራ በመፈለግ፣ሕዝቧ ሁሉ በሥቃይ ይጮኻል፤በሕይወት ለመኖር፣የከበረ ሀብታቸውን በምግብ ይለውጣሉ፤“አቤቱ እግዚአብሔር ሆይ፤ አስበኝ፤ ተመልከተኝም፤እኔ ተዋርጃለሁና።”