21. ይልቁንም፣“ስለ እርሱ ያልተነገራቸው ያያሉ፤ያልሰሙም ያስተውላሉ” ተብሎ እንደ ተጻፈ ነው።
22. በዚህም ምክንያት ወደ እናንተ እንዳልመጣ ብዙ ጊዜ ተከለከልሁ።
23. አሁን ግን በእነዚህ አካባቢዎች የምሠራው ስለሌለ፣ ከብዙ ዓመታት ጀምሮ እናንተን ለማየት እናፍቅም ስለ ነበር፣
24. ይህን ዕቅድ ወደ እስጳንያ በምሄድበት ጊዜ ልፈጽመው አስባለሁ። በማልፍበትም ጊዜ ልጐበኛችሁና ከእናንተ ጋር ለጥቂት ጊዜ ቈይቼ ናፍቆቴን ከተወጣሁ በኋላ በጒዞዬ እንደም ትረዱኝ ተስፋ አደርጋለሁ።
25. አሁን ግን በዚያ የሚገኙትን ቅዱሳን ለማገልገል ወደ ኢየሩሳሌም በመጓዝ ላይ ነኝ።
26. ምክንያቱም መቄዶንያና አካይያ፣ በኢየሩሳሌም ካሉት ቅዱሳን መካከል የሚገኙትን ድኾች ለመርዳት ተነሣሥተዋልና።