7. ማስተዋል የጐደለውን ወጣት፣ብስለት ከሌላቸው መካከል አየሁት፤ከጎልማሶችም መካከል ለየሁት።
8. የቤቷን አቅጣጫ ይዞ፣በቤቷ ማእዘን አጠገብ ባለው መንገድ ያልፍ ነበር፤
9. ቀኑ መሸትሸት ሲል፣በውድቅት ሌሊት፣ በጽኑ ጨለማ።
10. ከዚያም አንዲት ሴት ልታገኘው ወጣች፤እንደ ዝሙት አዳሪ ለብሳ፣ ለማሳሳት ታጥቃ።
11. ጯኺና ማን አለብኝ ባይ ናት፤እግሮቿ አርፈው ቤት አይቀመጡም፤
12. አንዴ በመንገድ፣ አንዴ በአደባባይ፤በየማእዘኑም ታደባለች።
13. አፈፍ አድርጋ ይዛ ሳመችው፤ኀፍረቷንም ጥላ እንዲህ አለችው፤