ምሳሌ 6:7-23 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

7. አዛዥ የለውም፤አለቃም ሆነ ገዥ የለውም፤

8. ሆኖም ግን በበጋ ምግቡን ያከማቻል፤በመከርም ወቅት ቀለቡን ይሰበስባል።

9. አንተ ታካች፤ እስከ መቼ ትተኛለህ?ከእንቅልፍህስ መቼ ትነሣለህ?

10. ጥቂት ማንቀላፋት፤ ጥቂት ማንጐላቸት፤እጅን አጣጥፎ “እስቲ ጥቂት ልረፍ” ማለት፤

11. ድኽነት እንደ ወንበዴ፣ዕጦትም መሣሪያ እንደ ታጠቀ ሰው ከተፍ ይልብሃል።

12. ወሮበላና ጨካኝ፣ነውረኛ አንደበቱን ይዞ የሚዞር፣

13. በዐይኑ የሚጠቅስ፣በእግሩ ምልክት የሚሰጥ፣በጣቶቹ የሚጠቊም፣

14. በልቡ ተንኰል ክፋትን የሚያውጠነጥን፣ምንጊዜም ጠብ ይጭራል።

15. ስለዚህ በቅጽበት መዓት ይወርድበታል፤በድንገት ይጠፋል፤ መዳኛም የለውም።

16. እግዚአብሔር የሚጠላቸው ስድስት ነገሮች አሉ፤የሚጸየፋቸውም ሰባት ናቸው፤ እነርሱም፦

17. ትዕቢተኛ ዐይን፣ሐሰተኛ ምላስ፣ንጹሕ ደም የሚያፈሱ እጆች፣

18. ክፋትን የሚያውጠነጥን ልብ፣ወደ ክፋት የሚቻኰሉ እግሮች፣

19. በውሸት ላይ ውሸት የሚጨምር ሐሰተኛ ምስክር፣በወንድማማቾች መካከል ጠብን የሚጭር ሰው።

20. ልጄ ሆይ፤ የአባትህን ትእዛዝ አክብር፤የእናትህንም ትምህርት አትተው።

21. ምንጊዜም በልብህ አኑራቸው፤በዐንገትህም ዙሪያ እሰራቸው።

22. በምትሄድበት ሁሉ ይመሩሃል፤በምትተኛበት ጊዜ ይጠብቁሃል፤በምትነቃበት ጊዜም ያነጋግሩሃል።

23. እነዚህ ትእዛዞች መብራት ናቸውና፤ይህችም ትምህርት ብርሃን፣የተግሣጽ ዕርምትም የሕይወት መንገድ ናት፤

ምሳሌ 6