ምሳሌ 5:8-16 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

8. መንገድህን ከእርሷ አርቅ፤በደጃፏም አትለፍ፤

9. ይኸውም ጒብዝናህን ለሌሎች፣ዕድሜህንም ለጨካኞች እንዳትሰጥ ነው፤

10. ባዕዳን በሀብትህ እንዳይፈነጥዙ፣ልፋትህም የሌላውን ሰው ቤት እንዳያበለጽግ ነው።

11. በዕድሜህ መጨረሻ ታቃሥታለህ፤ሥጋህና ሰውነትህ ሲከዳህ።

12. እንዲህም ትላለህ፤ “ምነው! ተግሣጽን ጠላሁ፤ልቤስ ምነው! መታረምን ናቀ፤

13. የመምህሮቼን ቃል አልሰማሁም፤አሰልጣኞቼንም አላደመጥኋቸውም፤

14. በመላው ጉባኤ ፊት፣ወደ ፍጹም ጥፋት ተቃርቤአለሁ።”

15. ከገዛ ማጠራቀሚያህ ውሃ፣ከገዛ ጒድጓድህም የሚፈልቀውን ውሃ ጠጣ።

16. ምንጮችህ ተርፈው ወደ ሜዳ፣ወንዞችህስ ወደ አደባባይ ሊፈሱ ይገባልን?

ምሳሌ 5