ምሳሌ 5:4-8 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

4. በመጨረሻ ግን እንደ እሬት ትመራለች፤ሁለት አፍ እንዳለውም ስል ሰይፍ ትሆናለች።

5. እግሮቿ ወደ ሞት ይወርዳሉ፤ርምጃዎቿም በቀጥታ ወደ ሲኦል ያመራሉ።

6. ስለ ሕይወት መንገድ ደንታ የላትም፤መንገዶቿ ዘወርዋራ ናቸው፤ ለእርሷ ግን አይታወቃትም።

7. እንግዲህ፣ ልጆቼ ሆይ፤ አድምጡኝ፤ከምነግራችሁ ቃል ፈቀቅ አትበሉ።

8. መንገድህን ከእርሷ አርቅ፤በደጃፏም አትለፍ፤

ምሳሌ 5