ምሳሌ 24:3-11 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

3. ቤት በጥበብ ይሠራል፤በማስተዋልም ይጸናል፤

4. በዕውቀትም ውድና ውብ በሆነ ንብረት፣ክፍሎቹ ይሞላሉ።

5. ጠቢብ ሰው ታላቅ ኀይል አለው፤ዕውቀት ያለውም ሰው ብርታትን ይጨምራል፤

6. ጦርነት ለመግጠም መልካም ምክር፣ድል ለማድረግም ብዙ አማካሪዎች ያስፈልጋሉ።

7. ጥበብ ለተላላ በጣም ሩቅ ናት፤በከተማዪቱ በር ሸንጎ ላይም መናገር አይችልም።

8. ክፋት የሚያውጠነጥን፣‘ተንኰለኛ’ በመባል ይታወቃል።

9. የተላላ ዕቅድ ኀጢአት ነው፤ሰዎችም ፌዘኛን ይጸየፋሉ።

10. በመከራ ጊዜ ፈራ ተባ ካልህ፣ዐቅምህ ምንኛ ደካማ ነው!

11. ወደ ሞት የሚነዱትን ታደጋቸው፤እየተጐተቱ ለዕርድ የሚሄዱትን አድናቸው።

ምሳሌ 24