ምሳሌ 15:8-15 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

8. እግዚአብሔር የክፉዎችን መሥዋዕት ይጸየፋል፤የቅኖች ጸሎት ግን ደስ ያሰኘዋል።

9. እግዚአብሔር የክፉዎችን መንገድ ይጸየፋል፤ጽድቅን የሚከታተሉትን ግን ይወዳቸዋል።

10. ከመንገድ የሚወጣ ሰው ጥብቅ ቅጣት ይጠብቀዋል፤ዕርምትን የሚጠላ ይሞታል።

11. ሲኦልና የሙታን ዓለም በእግዚአብሔር ፊት የተገለጡ ናቸው፤የሰዎች ልብ ማየቱን ያህል የታወቀ ነው!

12. ፌዘኛ መታረምን ይጠላል፤ጠቢባንንም አያማክርም።

13. ደስተኛ ልብ ፊትን ያፈካል፤የልብ ሐዘን ግን መንፈስን ይሰብራል።

14. አስተዋይ ልብ ዕውቀትን ይሻል፤የተላላ አፍ ግን ቂልነትን ያመነዥካል።

15. የተጨቈኑ ሰዎች ዘመናቸው ሁሉ የከፋ ነው፤በደስታ የተሞላ ልብ ግን የማይቋረጥ ፈንጠዝያ አለው።

ምሳሌ 15