ምሳሌ 15:4-8 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

4. ፈውስ የምታመጣ ምላስ የሕይወት ዛፍ ናት፤አታላይ ምላስ ግን መንፈስን ትሰብራለች።

5. ተላላ የአባቱን ምክር ይንቃል፤መታረምን የሚቀበል ግን አስተዋይነቱን ያሳያል።

6. የጻድቃን ቤት በብዙ ሀብት የተሞላ ነው፤የክፉዎች ገቢ ግን መከራን ታመጣባቸዋለች።

7. የጠቢባን ከንፈር ዕውቀትን ታስፋፋለች፤የተላሎች ልብ ግን እንዲህ አይደለም።

8. እግዚአብሔር የክፉዎችን መሥዋዕት ይጸየፋል፤የቅኖች ጸሎት ግን ደስ ያሰኘዋል።

ምሳሌ 15