ምሳሌ 15:4-11 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

4. ፈውስ የምታመጣ ምላስ የሕይወት ዛፍ ናት፤አታላይ ምላስ ግን መንፈስን ትሰብራለች።

5. ተላላ የአባቱን ምክር ይንቃል፤መታረምን የሚቀበል ግን አስተዋይነቱን ያሳያል።

6. የጻድቃን ቤት በብዙ ሀብት የተሞላ ነው፤የክፉዎች ገቢ ግን መከራን ታመጣባቸዋለች።

7. የጠቢባን ከንፈር ዕውቀትን ታስፋፋለች፤የተላሎች ልብ ግን እንዲህ አይደለም።

8. እግዚአብሔር የክፉዎችን መሥዋዕት ይጸየፋል፤የቅኖች ጸሎት ግን ደስ ያሰኘዋል።

9. እግዚአብሔር የክፉዎችን መንገድ ይጸየፋል፤ጽድቅን የሚከታተሉትን ግን ይወዳቸዋል።

10. ከመንገድ የሚወጣ ሰው ጥብቅ ቅጣት ይጠብቀዋል፤ዕርምትን የሚጠላ ይሞታል።

11. ሲኦልና የሙታን ዓለም በእግዚአብሔር ፊት የተገለጡ ናቸው፤የሰዎች ልብ ማየቱን ያህል የታወቀ ነው!

ምሳሌ 15