1. ተግሣጽን የሚወድ ዕውቀትን ይወዳል፤መታረምን የሚጠላ ግን ደነዝ ነው።
2. መልካም ሰው ከእግዚአብሔር ዘንድ ሞገስ ያገኛል፤ተንኰለኛውን ግን እግዚአብሔር ይፈርድበታል።
3. ሰው በክፋት ላይ ተመሥርቶ ሊጸና አይችልም፤ጻድቃን ግን ከቦታቸው አይነቃነቁም።
4. መልካም ሴት ለባሏ ዘውድ ናት፤አሳፋሪ ሚስት ግን ዐጥንቱ ውስጥ እንዳለ ንቅዘት ናት።
5. የጻድቃን ሐሳብ ቀና ነው፤የክፉዎች ምክር ግን ሸር አለበት።
6. የክፉዎች ቃል ደም ለማፍሰስ ታደባለች፤የቅኖች ንግግር ግን ይታደጋቸዋል።
7. ክፉ ሰዎች ይገለበጣሉ፤ ድራሻቸውም ይጠፋል፤የጻድቃን ቤት ግን ጸንቶ ይኖራል።