42. ሁሉም በልተው ጠገቡ፤
43. ደቀ መዛሙርቱም ከተበላው እንጀራና ዓሣ፣ ዐሥራ ሁለት መሶብ ሙሉ ፍርፋሪ አነሡ።
44. እንጀራውንም የበሉት አምስት ሺህ ወንዶች ነበሩ።
45. ወዲያውም እርሱ ሕዝቡን እያሰናበተ ሳለ፣ ደቀ መዛሙርቱ በጀልባ ወደ ቤተ ሳይዳ ቀድመውት እንዲሻገሩ አዘዛቸው፤
46. ከዚያም ትቶአቸው ሊጸልይ ወደ ተራራ ወጣ።
47. በመሸም ጊዜ ጀልባዋ ባሕሩ መካከል ነበረች፤ እርሱም ብቻውን በምድር ላይ ነበር።