ማርቆስ 14:64-67 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

64. ስድቡን ሰምታችኋል፤ ታዲያ፣ ምን ይመስላችኋል?”፤እነርሱም ሞት ይገባዋል በማለት በአንድ ቃል ፈረዱበት።

65. በዚህ ጊዜ አንዳንዶቹ ይተፉበት ጀመር፤ ዐይኑንም ሸፍነው በጡጫ እየመቱት፣ “እስቲ ትንቢት ተናገር!” ይሉት ነበር። ሎሌዎችም በጥፊ እየመቱ ወሰዱት።

66. ጴጥሮስ በግቢው ውስጥ በታችኛው በኩል ሳለ፣ ከሊቀ ካህናቱ ገረዶች አንዲቱ መጣች፤

67. ጴጥሮስ እሳት ሲሞቅ አይታ ትኵር ብላ ተመለከተችውና፣“አንተም ከናዝሬቱ ኢየሱስ ጋር ነበርህ” አለችው።

ማርቆስ 14