13. ለኀጢአተኞች ጒድጓድ እስኪማስላቸው ድረስ፣እርሱን ከመከራ ታሳርፈዋለህ።
14. እግዚአብሔር ሕዝቡን አይጥልምና፤ርስቱንም አይተውም።
15. ፍርድ ተመልሶ በጽድቅ አሠራር ላይ ይመሠረታል፤ልባቸውም ቀና የሆነ ሁሉ ይከተሉታል።
16. ክፉዎችን የሚቋቋምልኝ ማን ነው?ከክፉ አድራጊዎችስ ጋር የሚሟገትልኝ ማን ነው?
17. እግዚአብሔር ረዳቴ ባይሆን ኖሮ፣ነፍሴ ወደ ዝምታው ዓለም ፈጥና በወረደች ነበር።