መዝሙር 89:26-37 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

26. እርሱም፣ ‘አንተ አባቴ ነህ፤አምላኬና መዳኛ ዐለቴም ነህ’ ብሎ ይጠራኛል።

27. እኔም ደግሞ በኵሬ አደርገዋለሁ፤ከምድር ነገሥታትም በላይ ከፍ ይላል።

28. ምሕረቴንም ለዘላለም ለእርሱ እጠብቃለሁ፤ከእርሱ ጋር የገባሁት ኪዳንም ጸንቶ ይኖራል።

29. የዘር ሐረጉን ለዘላለም፣ዙፋኑንም በሰማያት ዕድሜ ልክ አጸናለሁ።

30. “ልጆቹ ሕጌን ቢተዉ፣ደንቤን ባይጠብቁ፣

31. ሥርዐቴን ቢጥሱ፣ትእዛዜንም ባያከብሩ፣

32. ኀጢአታቸውን በበትር፣በደላቸውን በጅራፍ እቀጣለሁ።

33. ምሕረቴን ግን ከእርሱ አላርቅም፤ታማኝነቴንም አላጓድልበትም።

34. ኪዳኔን አላፈርስም፤ከአፌ የወጣውንም አላጥፍም።

35. አንድ ጊዜ በቅድስናዬ ምያለሁና፣ዳዊትን አልዋሸውም።

36. የዘር ሐረጉ ለዘላለም፣ዙፋኑም በፊቴ እንደ ፀሓይ ጸንቶ ይኖራል፤

37. በሰማይ ታማኝ ምስክር ሆና እንደምትኖረው፣እንደ ጨረቃ እርሱ ለዘላለም ይመሠረታል።” ሴላ

መዝሙር 89