11. መኳንንታቸውን እንደ ሔሬብና እንደ ዜብ፣መሳፍንታቸውንም ሁሉ እንደ ዛብሄልና እንደ ስልማና አድርጋቸው፤
12. እነዚህም፣ “የእግዚአብሔርን የግጦሽ ቦታ፣ወስደን የግላችን እናድርግ” የሚሉ ናቸው።
13. አምላኬ ሆይ፤ በዐውሎ ነፋስ እንደሚነዳ ትቢያ፣በነፋስም ፊት እንዳለ ገለባ አድርጋቸው።
14. እሳት ደንን እንደሚያጋይ፣ነበልባልም ተራራን እንደሚያቃጥል፣
15. እንዲሁ በሞገድህ አሳዳቸው፤በማዕበልህም አስደንግጣቸው።
16. እግዚአብሔር ሆይ፤ ስምህን ይሹ ዘንድ፣ፊታቸውን በዕፍረት ሙላው፤
17. ለዘላለም ይፈሩ፤ ይታወኩም፤በውርደትም ይጥፉ።
18. ስምህ እግዚአብሔር የሆነው አንተ ብቻ፣በምድር ሁሉ ላይ ልዑል እንደሆንህ ይወቁ።